
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስቀድሞ ከመከላከል እንዲሁም አደጋዎች ሲገጥሙ ደግሞ ሰብአዊነትን መሰረት ያደረገ አፋጣኝ ምላሽ በመስጠት ከመንግስት ተቋማት ጋር በመሆን የረዥም ጊዜ ሥራ ሲሰሩ መቆየታቸው ታሪክ የሚዘክረው ነው።
ማክሰኞ ሀምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረገ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝደንት አቶ አህመድ ሁሴን ” ሰብዓዊነት የሲቪል ማህበራት ዋነኛ መገለጫ ነው፡፡ ሰብዓዊነት ድንበር የለውም። እኛም ዛሬ በዚህ ስፍራ የተገናኘነው አረንጓዴ ልማትን ከአካባቢያችንና ከሀገራችን በመጀመር በደን መራቆት ምክንያት መላው የሰው ልጆች ከተጋረጠባቸው ከፍተኛ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖ ለመታደግ ችግኞችን በመትከል ሰብዓዊ ሃላፊነታችንን ለመወጣት ነው” ብለዋል። አቶ አህመድ አክለውም የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ከልጅ አስከ አዋቂ የሚሳተፍበት መልካም ተግባር በመሆኑ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከሚሰሩት ስራ ጋር በማቀናጀት ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል።
የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ሀላፊዎች የምክር ቤቱ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት እና የምክር ቤቱ ጽህፈት ቤት ሰራተኞች ከተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመሆን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ ተሳትፈዋል።
የሲቪል ማህበረሰሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ዳይሬክተር ጀነራል አቶ ሳምሶን ቢራቱ በመልዕክታቸው የዘንድሮው አረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ‹‹በመትከል ማንሰራራት›› በሚል መሪ ቃል በሃገር አቀፍ ደረጃ መጀመሩን አንስተው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም አረንጓዴ አሻራቸውን ለማኖር በመገኘታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
የምክር ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ተረፈ ደጌቲ ለዘርፉ ያስተላለፉት መልዕክት አካባቢንም ሆነ ሀገርን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንደተለመደው በመተባበር ችግኝ ከመትከል ባለፈ የተተከለውን ከመንከባበቡ ረገድም የሲቪል ማህበረሰብ ዘርፉ እና ሁሉም አካል መጠንከር እንዳለበት አስምረውበታል።
Civil society organizations have a continuing culture of working with government institutions to prevent disasters caused by climate change and to respond to disasters based on humanitarian principles.
During the tree planting session held on Tuesday, July 15, 2025, Ahmed Hussen, President of the Ethiopian Civil Society Organizations Council, said, “Humanity is the main characteristic of civil society. Humanity has no borders. We are here today to fulfill our human responsibility by planting trees to protect all humanity from the severe impacts of climate change that are being faced in the world due to deforestation.” He added that the green legacy initiative is a commendable activity welcomes the involvement of each citizen regardless of age groul and should be implemented in coordination with the work of civil society organizations.
Officials from Authority for Civil Society Organization (ACSO), ECSOC’s Executive Committee members and staff of the Council’s Secretariat participated in the tree planting program together with various civil society organizations.
Director General of ACSO, Samson Biratu, in a speech said that this year’s tree planting program was launched nationwide under the theme “Regeneration through Planting” and thanked civil society organizations for their presence to leave their green footprints.
Executive Director of ECSOC Terefe Degeti extend a call to all parties and civil society sector to join hands to improve the environment and the country, not only by planting trees, but also by taking care of what has been planted.
